ስለ የዓለም ዋንጫ የኢትዮጵያው ቅጂ ሙዚቃ የተሰጠ መግለጫ

ባለፉት ወራቶች ቴዎድሮስ ካሳሁን ወይም “ቴዲ አፍሮ” ከኮካ ኮላ እና በስፋት ሲወራ ከከረመው  የዓለም ዋንጫ የኢትዮጵያው ቅጂ ሙዚቃ ጋር ስለነበረው ግንኙነት ያለንን አቋም እንድንገልፅ በሚጎርፍልን ጥያቄዎች ምክኒያት ከፍተኛ ጫና ስደረግብን ቆይተናል፡፡ በበኩላችን በተገባው የውል ስምምነት ላይ የግንኙነቱን ሚስጥራዊነት ለመጠበቅ ቃል ኪዳን የገባን እና ማክበር የነበረብን ቢሆንም ቅሉ የቴዲ አፍሮ እና የኮካ ግንኙነት ወሬ እንዴት አፈትልኮ ወጥቶ ህዝብ እንዲያውቀው እንደቻለ ቢያስገርመንም አሁን ለመገንዘብ እንደቻልነው ቴዲ ከኮካ ጋር ያለውን ግንኙነት ኢትዮፒካ ሊንክ በተሰኘ የአገር ውስጥ የኤፍ ኤም ሬዲዮ የመዝናኛ ፕሮግራም አዘጋጆች አማካኝነት ያወጀው እና በሚያስገርም ሁኔታ ለኮካ የቲቪ ሥራም አድናቆቱን በመስጠት ያረጋገጠው የኮካ ኮላ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ብራንድ ሥራ አስኪያጅ የሆነው አቶ ምስክር ሙሉጌታ መሆኑን መረዳት ችለናል፡፡

ያለጥርጥር በኮካ ኮላ ስም ቴዲ አፍሮ ለኮካ የቴሌቪዥን ስራ በማገናኘት እና በዓለም ዋንጫ የኢትዮጵያው ቅጂ ሙዚቃ ላይ ተሳታፊ እንዲሆን ተነሳሽነቱን የወሰደው የብራንዱ ሥራ አስኪያጅ ነበር፡፡ እኛም ጥያቄውን ውድ አገራችንን በመላው የአለም ዋንጫ ተመልካቾች ዘንድ   አዎንታዊ ገፅታ የትኩረት እይታ ስር የሚያውላት በመሆኑ እና በዚህ በጉጉት በሚጠበቀው ታላቅ ዓለምአቀፍ የስፖርት ክንዋኔ ግዙፍ ቁጥር ያለው የዓለም ህዝብ ዘንድ የአገራችንን እና የህዝባችንን መልካም ገፆች ለማሳየት የበኩላችንን አስተዋፅኦ ለምናደርገው ጥረት ሲባል በፍፁም ቅን ልቦና ተቀብለናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በሚለቀቅበት ወቅት የዓለም ዋንጫ የኢትዮጵያው ቅጂ ሙዚቃ የቴዲ አፍሮን ዓለም አቀፍ እውቅና እና ዝና፣ የሥነ ጥበብ ገፅታ እና ስብዕና የበለጠ ከፍ እንደሚያደርገው እና እንደሚያጠናክረው በሚገባ እንገነዘባለን፡፡

ለታፈረችው አገራችን፣በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ለሚገኙት ለውድ አድናቂዎቻችንና ለሰው ልጆች ሁሉ ባለን የማይታጠፍ ታማኝነት በኮካ ፕሮጄክት ተሳታፊ መሆናችን ትክክለኛ እና አግባብነት የነበረው ውሳኔ ነው፡፡ በዚህም ምክኒያት የዓለም ዋንጫ የኢትዮጵያው ቅጂ ሙዚቃ የቴሌቪዥን ቀረፃው የተሻለ ውጤታማነት ይኖረው ዘንድ ቴዲ አፍሮ በበኩሉ አቅሙ የቻለውን ያህል ጊዜውን፣ጉልበቱን እና ስነ ጥበባዊ ክህሎቱን በመጠቀም አስፈላጊውን ጥረት አድርጓል፡፡ በኮካ ሰቱዲዮ ፕሮጄክት ተሳታፊ የመሆኑ ዋነኛው ፋይዳ አለም አቀፍ ተዋቂነት ባለው ብራንድ በመጠቀም የኢትዮጵያን አዎንታዊ ገፅታ ለማጉላት የመላውን ዓለም ህዝብ ትኩረት ለመሳብ የሚያስችል ከባድ ያለ ተልዕኮ ለመወጣት እንጂ የንግድ ዕቃ በማስተዋወቅ ለሚያስገኘው እምብዛም ያልሆነ ጥቅም አልነበረም፡፡

በመሆኑም ሙዚቃ ነክ ንብረቶችን በማዘጋጀት እና በማሰራጨት የተለያዩ አገልግሎቶችን ለኮካ ኮላ የማዕከላዊ ምስራቅ እና ምዕራብ አፍሪካ ለመስጠት ወኪል የሆነው ማንዳላ ቲቪ የዝግጅት ሥራ አስኪያጅ ሚ/ር ዴቪድ ሣንደር፣ በኮክ ስቱዲዮ የተሰራው የቴዲ አፍሮ ስራ በሚያስደንቅ እና በተሳካ ሁኔታ መከናወኑን የሚገልፀውን ስሜት ቀስቃሽ እና አጓጊ ዜና እና ብስራት የተቀበልነው በከፍተኛ ክብር፣ ኩራት እና እርካታ ሲሆን ይህው ሰው ከዚያም አልፎ “የአለም ዋንጫ ቪዲዮው ተዘጋጅቶና ተከፋፍሎ ምናልባት በጥር ወር በኮካ ኮላ ይለቀቃል” በማለት አረጋግጦልናል፡፡ ከሥራው መጠናቀቅ በኋላ በውጤቱ የተደሰቱት የቴሌቪዢን አዘጋጆች እዚያው ላይ ቴዲ አፍሮ በአንድ የኮካ የሙዚቃ አልበም ተሳታፊ ይሆን ዘንድ ያቀረቡለትን ጥያቄ ወዲያውኑ በመቀበል በሥራው የተሳተፈ ሲሆን ይህም ስራ “የአዲስ አመት  ክንውን” ሆኖ ባለፈው “ታህሳስ 22 ቀን በአራት አገሮች ከምሽቱ 2 ሰዓት ጀምሮ እንዲጫወት ተደርጓል፡፡”

ከበርካታ ቀናት በኋላ፣ የዓለም ዋንጫ የኢትዮጵያው ቅጂ ሙዚቃ መለቀቅ በጉጉት በምንጠባበቅበት ወቅት አቶ ምስክር የተጠናቀቀውን የዓለም ዋንጫ የኢትዮጵያው ቅጂ ሙዚቃ እንድንመለከተው የጋበዘን ሲሆን በአርቲስቱ ሥራም እንደ ቴሌቪዢን አዘጋጆች  ሁላችንም በጣም ደስተኛ ነበርን፡፡

ከጥቂት ጊዜ ባኃላ ግን ከባዶ መነሻነት አስደናቂ መጠማዘዝ ያሳየው አቶ ምስክር ፍርሐት በሞላው ድባብ በተጠናቀቀው ሥራ ላይ የነበረው የቴዲ አፍሮ ተሳትፎ እና ሽፋን “ዝናውን የሚመጥን አይደለም” በሚል የተጠናቀቀው ሙዚቃ እንዳይለቀቅ ድጋፍ እና ተቀባይነት ለማግኘት የሙከራ ጥረት አደረገ፡፡ ይህንን አቋሙን እንቀበልለት ዘንድ ለማሳመን ያደረጋቸው ሁሉም ጉዞዎች እና ኩነቶች በጉዳዩ ላይ “የቴሌኮንፈረንስ” እንዲካሄድ በመጠየቅ ከመታጀቡ በተጨማሪ በእርሱ አስተሳሰብ “ውድቀት” ሊሆን ስለሚችለውና የያዘውን አቋም አስመልክቶ ቴዲ አፍሮ ለህዝብ እንዳይገልፅበት እንድንታቀብ አስከማስፈራራት የደረሰ ነበር፡፡ ከዚህም በላይ ከመነሻው ጀምሮ በኮክ ፕሮጄክት ተሳታፊ እንዳልነበረ እና የኮካ ወኪል ከሆነው ከማንዳላ ቲቪ ጋር እንድንገናኝ ለማድረግ እና እኛን ለማሳመን እንዳልተሳተፈ ሁሉ አቶ ምስክር ከስራው ጋር በተያያዘ ከኮካ ኮላ ጋር የነበረን ግንኙነት በማስተባበል ራሱን በማራቅ ብሔራዊ እና ህዝባዊ ሃላፊነቶችን በተጋረደ ጠባብ የግል ጥቅም ለመለወጥ በፈፀመው አሳፋሪ፣ አገር ወዳድነት በሌለው የፈሪ ተግባሩ  ኃላፊነትን ላለመሸከም በማሰብ ራሱን የማሸሽ እንቅስቃሴ አደርጓል፡፡

በኮካ ሰቱዲዮ የዝግጅት ሥራ አስኪያጅ በኩል ከቴክኒክ አኳያ የተጠናቀቀው ስራ የላቀ ጥራት እንዳለው በተደጋጋሚ ተረጋግጦልናል፡፡ በመሆኑም የዓለም ዋንጫ የኢትዮጵያው ቅጂ ሙዚቃን ይዞ በማቆየት እንዳይከፋፈል እና እንዳይለቀቅ የተደረገበት ምክኒያት እና የመጨረሻ ውሳኔ ከአርቲስቱ ወይም ከሥራ አስኪያጁ ጋር ምንም ውይይት ሳይደረግ እና ሳያውቁት በአቶ ምስክር ሙሉጌታ እና በኮካ ወኪል ማንዳላ ቲቪ የተሰጠ የጋራ ውሳኔ ነው፡፡

የተጠናቀቀው ሥራ ተሰራጭቶ እንዲለቀቅ በተደጋጋሚ የጠየቅን ቢሆንም፣ ከወኪሉ በመጨረሻ ላይ ያገኘነው ምላሽ ግን “በዚህ ደረጃ የዓለም ዋንጫ የኢትዮጵያው ቅጂ ሙዚቃ ለጊዜው አንለቀውም” በሚል የተገለፀልን ከመሆኑ በላይ በእኛ ዘንድ የተፈጠረውን ሃያል ቁጣ በማባበል ለማቀዝቀዝ የሚሞክር እና ሥራውን ወደፊት ሊለቁት እንደሚችሉ ለማሳመን  የሚጥር ማታለያ እና ለምንወዳት አገራችን፣ ለሁሉም ራሱን ለሚያከብር ኢትዮጵያዊ፣ በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ የአገር ውስጥ እና የውጪ አድናቂዎች እና ለአርቲስቱ በቁስል ላይ እንጨት የመስደድ ያህል ሆኖብናል፡፡

በበኩላችን በተጠናቀቀው ሥራ ላይ ስለተወሰደው ተገማችነት ላልነበረው የዱብዳ እርምጃ ለአቅረብነው ጥያቄ ማብራሪያ እና ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው በርካታ ጥረት ትኩርት የተነፈገው ወይንም ከነጭራሹ ችላ ከመባሉ ውጪ ምላሽ የተሰጠውም ትዕግስታችን ከተሟጠጠ በኋላ ነበር፡፡

በመጨረሻም ምንም እንኳን በጉዳዩ ጭብጥ ዙሪያ በሁለቱም ወገኖች ዘንድ ስለተያዘው አቋም የተወሰነ መግባባት ላይ ለመድረስ ቴሌኮንፈረንስ የሚመለከታቸው ወገኖች እንደሚገኙበት ቃል ተግብቶበት የተዘጋጀ ቢሆንም ውይይቱ ሙያዊ በሆነ መልኩ ያልተዘጋጀ፣ ግልፅነት የጎደለው፣ አለመግባባት እንዳይከሰት ለማድረግ የጋራ መፍትሔ ለመሻት ሳይሆን ቅንነት በጎደለው መልኩ ይኛን ሐሳብ ለመረዳት ነበር፡፡ ቴሌኮንፈረንሱ ሆነ ተብሎ ህጋዊ ወኪል የሆነውን ሥራ አስኪያጃችንን በጭብጦቹ ላይ ለመወያየት እንዳይሳተፍ በማግለል መካሄዱ በራሱ ሂደቱ በቅን ልቦና ላይ ያለተመሰረተ መሆኑ ግልፅ ማስረጃ ነው፡፡

በመሆኑም የአርቲስቱ አድናቂ ለሆኑት ኢትዮጵያዊያን እና የውጪ አገር ዜጎች በሙሉ ከኮካ ኮላ ጋር የነበረንን ግንኙነት የቆረጥን መሆናችንን ለመግለፅ መገደዳችን እያዘንን ስንገልፅ የዓለም ዋንጫ እስከሚከፈትበት ዕለት ድረስ ኮካ ኮላ የወሰደውን እርምጃ በድጋሚ እንዲያጤነው ያደርግ ዘንድ በተደጋጋሚ ጥሪያችንን ስናቀርብ ብሔራዊ ጠርዝ ባለው እና በውድ አገራችን፣ በህዝባችን እና አድናቂዎቻችን ላይ ጭምር የተቃጣውን የፈሪ፣ እና አገር ወዳድነት የጎደለውን አሳፋሪ የክህደት እና ክብር የሚያጎደፈውን ተግባር ግን ይቅር ላለማለት ወስነናል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ አስከመጨረሻው ዕለት ድረስ ኮካ ኮላ የተጠናቀቀውን ሥራ እንዲያሰራጨው እና እንዲለቀው ግፊት ማድረጋችንን እንደምንቀጥልበት ለአድናቂዎቻችንን እያረጋገጥን ከዚሁ ጎን ለጎንም ከሁኔታዎች ጋር አግባብነት ያላቸውን ሰላማዊ እርምጃዎችንም በመውሰድ የሁለቱንም ወገኖች ገፅታን እና ጥቅምን የሚጎዳ ማናቸውም ውዝግብ በማስቀረት በአድናቂዎቻችን የተጣሉብንን አደራ መተማመን እና እምነትን ለመመለስ የሚያስችል እርምጃ የምንወስድ መሆናችንን እንገልፃለን፡፡

3 Comments

  1. Teddy,
    YOU are blessed. You are LOVE. You are Ethiopia. Remember, it is not possible to expect anything positive from same people who are trying to destroy the country. But I can assure you that Ethiopia will not be destroyed and any effort that is designed to degrade its heroes such as YOU among others, will not succeed. GOD bless Ethiopia!

  2. Teddy, you are always our hero and icon. Whether this damn company Coca Cola canceled your world cup work or not don’t bring any change. You are living with our heart. Love always shall win. We Love u!!!!!!!!!!! We understand a lot of things are wavering around u and your work to silence you not to preach about LOVE and UNITY! GOD Be with YOU!!!!!!!!

  3. Tedy, you are our Hero and Icon!!!!! We really Love you. Whether this damn company (Coca Cola) cancelled your valuable work or not, don’t bring any change. You are always in our heart. You are preaching and sacrificing, preaching about LOVE and UNITY. LOVE always shall win. GOD will be with YOU!!!!!!!!

Leave a Reply to Wassihun Masresha Cancel reply

Your email address will not be published.


*


This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.